ترجمة معاني سورة الرحمن باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


አል-ረሕማን፤
آية رقم 2

ቁርኣንን አስተማረ፡፡
آية رقم 4

መናገርን አስተማረው፡፡
آية رقم 5

ፀሐይና ጨረቃ በተወሰነ ልክ (ይኼዳሉ)፡፡
آية رقم 6

ሐረግና ዛፍም (ለእርሱ) ይሰግዳሉ፡፡
آية رقم 7

ሰማይንም አጓናት፡፡ ትክክለኛነትንም ደነገገ፡፡
آية رقم 8

በሚዛን (ስትመዝኑ) እንዳትበድሉ፡፡
آية رقم 9

መመዘንንም በትክክል መዝኑ፡፡ ተመዛኙንም አታጉድሉ፡፡
آية رقم 10

ምድርንም ለፍጡሩ አደላደላት፡፡
آية رقم 11

በውስጧ እሸት ባለ ሺፋኖች የኾኑ ዘንባባዎችም ያሉባት ስትኾን፡፡
آية رقم 12

የገለባ ባለቤት የኾነ ቅንጣትም፡፡ ባለ መልካም መዐዛ ቅጠሎችም (ያሉባት ስትኾን)፡፡
آية رقم 13

(ሰዎችና ጋኔኖች ሆይ!) ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 14

ሰውን እንደ ሸክላ ከሚቅጨለጨል ደረቅ ጭቃ ፈጠረው፡፡
آية رقم 16

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 17

የሁለቱ ምሥራቆች ጌታ፤ የሁለቱ ምዕራቦችም ጌታ ነው፡፡
آية رقم 18

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 19

ሁለቱን ባሕሮች የሚገናኙ ሲኾኑ ለቀቃቸው፡፡
آية رقم 20

(እንዳይዋሐዱ) በመካከላቸው ጋራጅ አልለ፡፡ (አንዱ ባንዱ ላይ) ወሰን አያልፉም፡፡
آية رقم 21

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
آية رقم 22

ሉልና መርጃን ከሁለቱ ይወጣል፡፡
آية رقم 23

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 24

እንደ ጋራዎች ኾነው በባሕር ውስጥ የተሠሩት ተንሻለዮቹም (ታንኳዎች) የእርሱ ናቸው፡፡
آية رقم 25

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 26

በእርሷ (በምድር) ላይ ያለው ሁሉ ጠፊ ነው፡፡
آية رقم 27

የልቅናና የልግሥና ባለቤት የኾነው የጌታህ ፊትም ይቀራል፡፡ (አይጠፋም)፡፡
آية رقم 28

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በሰማያትና በምድር ውስጥ ያሉት ሁሉ ይለምኑታል፡፡ በየቀኑ ሁሉ እርሱ በሥራ ላይ ነው፡፡
آية رقم 30

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታሰተባብላላችሁ?›
آية رقم 31

እናንተ ሁለት ከባዶች (ሰዎችና ጋኔኖች) ሆይ! ለእናንተ (መቆጣጠር) በእርግጥ እናስባለን፡፡
آية رقم 32

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የጋኔንና የሰው ጭፍሮች ሆይ! ከሰማያትና ከምድር ቀበሌዎች መውጣትን ብትችሉ ውጡ፡፡ በስልጣን እንጅ አትወጡም፡፡ (ግን ስልጣን የላችሁም)
آية رقم 34

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 35

በሁለታችሁም ላይ ከእሳት ነበልባል፣ ጭስም ይላክባችኋል፡፡ (ሁለታችሁም) አትርረዱምም፡፡
آية رقم 36

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 37

ሰማይም በተሰነጠቀችና እንደ ጽጌረዳ፣ እንደታረበ ቆዳ በኾነች ጊዜ፤ (ጭንቁን ምን አበረታው)፡፡
آية رقم 38

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 40

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 41

ከሓዲዎች በምልክታቸው ይታወቃሉ፡፡ አናቶቻቸውንና ጫማዎቻቸውንም ይያዛሉ፡፡
آية رقم 42

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ፡፡
آية رقم 43

ይህቺ ያቺ አመጸኞች በእርሷ ያስተባብሉባት የነበረችው ገሀነም ናት (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 44

በእርሷና በጣም ሞቃት በኾነ ፍል ውሃ መካከል ይመላለሳሉ፡፡
آية رقم 45

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 46

በጌታውም ፊት መቆምን ለፈራ ሰው ሁለት ገነቶች አልሉት፡፡
آية رقم 47

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 48

የቀንዘሎች ባለ ቤቶች የኾኑ (ገነቶች አልሉት)፡፡
آية رقم 49

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 50

በሁለቱ ውስጥ የሚፈስሱ ሁለት ምንጮች አልሉ፡፡
آية رقم 51

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 52

በሁለቱ ውስጥ ከፍራፍሬዎች ሁሉ ሁለት ዓይነቶች (እርጥብና ደረቅ) አልሉ፡፡
آية رقم 53

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

የውስጥ ጉስጉሳቸው ከወፍራም ሐር በኾኑ ምንጣፎች ላይ የተመቻቹ ሲኾኑ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡ የሁለቱም ገነቶች ፍሬ (ለለቃሚ) ቅርብ ነው፡፡
آية رقم 55

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?

በውስጣቸው ከበፊታቸው (ከባሎቻቸው በፊት) ሰውም ጃንም ያልገሰሳቸው ዓይኖቻቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች (ሴቶች) አልሉ፡፡
آية رقم 57

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 58

ልክ ያቁትና መርጃን ይመስላሉ፡፡
آية رقم 59

ከጌታችሁም ጸጋዎቸ በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 61

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 62

ከሁለቱ ገነቶችም ሌላ ሁለት ገነቶች አልሉ፡፡
آية رقم 63

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?›
آية رقم 64

ከልምላሜያቸው የተነሳ ወደ ጥቁረት ያዘነበሉ ናቸው፡፡
آية رقم 65

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 66

በውስጣቸው ሁለት የሚንፏፉ ምንጮች አልሉ፡፡
آية رقم 67

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 68

በውስጣቸው ፍራፍሬ፣ ዘምባባም፣ ሩማንም አልለ፡፡
آية رقم 69

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 70

በውስጣቸው ጠባየ መልካሞች መልክ ውቦች (ሴቶች) አልሉ፡፡
آية رقم 71

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 72

በድንኳኖች ውስጥ የተጨጎሉ የዓይኖቻቸው ጥቁረትና ንጣት ደማቅ የኾኑ ናቸው፡፡
آية رقم 73

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 75

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባበላላችሁ?
آية رقم 76

በሚያረገርጉ አረንጓዴ ምንጣፎችና በሚያማምሩ ስጋጃዎች ላይ የተደላደሉ ሲኾኑ (ይቀመጣሉ)፡፡
آية رقم 77

ከጌታችሁም ጸጋዎች በየትኛው ታስተባብላላችሁ?
آية رقم 78

የግርማና የመክበር ባለቤት የኾነው ጌታህ ስም ተባረከ፡፡
تقدم القراءة