ترجمة معاني سورة المطفّفين باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡
آية رقم 2

ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡
آية رقم 3

ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡
آية رقم 4

እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?
آية رقم 6

ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡
آية رقم 7

በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 8

ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
آية رقم 9

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
آية رقم 10

ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡
آية رقم 11

ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡
آية رقم 12

በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡
آية رقم 13

አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡
آية رقم 15

ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡
آية رقم 16

ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡
آية رقم 17

ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡
آية رقم 18

በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 19

ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
آية رقم 20

የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡
آية رقم 21

ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡
آية رقم 22

እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 23

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡
آية رقم 24

በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡
آية رقم 25

ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡
آية رقم 26

ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡
آية رقم 27

መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡
آية رقم 28

ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡
آية رقم 29

እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡
آية رقم 30

በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡
آية رقم 31

ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡
آية رقم 32

ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡
آية رقم 33

በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡
آية رقم 34

ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡
آية رقم 35

በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡
آية رقم 36

ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡
تقدم القراءة