ترجمة معاني سورة القمر باللغة الأمهرية من كتاب الترجمة الأمهرية
محمد صادق
ﰡ
آية رقم 1
ﮬﮭﮮﮯ
ﮰ
ሰዓቲቱ (የትንሣኤ ቀን) ተቃረበች፤ ጨረቃም ተገመሰ፡፡
آية رقم 2
ተዓምርንም ቢያዩ (ከእምነት) ይዞራሉ፡፡ (ይህ) «ዘውታሪ ድግምት ነውም» ይላሉ፡፡
آية رقم 3
አስተባበሉም፡፡ ዝንባሌዎቻቸውንም ተከተሉ፡፡ ነገርም ሁሉ (ወሰን አለው)፤ ረጊ ነው፡፡
آية رقم 4
ከዜናዎችም በእርሱ ውስጥ መገሰጥ ያለበት ነገር በእርግጥ መጣላቸው፡፡
آية رقم 5
ﯪﯫﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
ሙሉ የኾነች ጥበብ (መጣቻቸው) ግን አስፈራሪዎቹ አያብቃቁም፡፡
آية رقم 6
ከነርሱም ዙር፡፡ ጠሪው (መልአክ) ወደ አስደንጋጭ ነገር የሚጠራበትን ቀን (አስታውስ)፡፡
آية رقم 7
ዓይኖቻቸው ያቀረቀሩ ኾነው፤ ፍጹም የተበተነ አንበጣ መስለው ከመቃብሮቹ ይወጣሉ፡፡
آية رقم 8
ወደ ጠሪው አንገቶቻቸውን ሳቢዎች ቸኳዮች ኾነው (ይወጣሉ)፡፡ ከሓዲዎቹ (ያን ጊዜ ምን ይላሉ?) «ይህ ብርቱ ቀን ነው» ይላሉ፡፡
آية رقم 9
ከእነርሱ በፊት የኑሕ ነገድ አስተባበለች፡፡ ባሪያችንንም (ኑሕን) አስተባበሉ፡፡ «ዕብድ ነውም» አሉ፡፡ ተገላመጠም፡፡
آية رقم 10
ﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
ጌታውንም «እኔ የተሸነፍኩ ነኝና እርዳኝ» ሲል ጠራ፡፡
آية رقم 11
ﭵﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
ወዲያውም የሰማይን ደጃፎች በሚንቧቧ ውሃ ከፈትን፡፡
آية رقم 12
የምድርንም ምንጮች አፈነዳን፡፡ ውሃውም (የሰማዩና የምድሩ) በእርግጥ በተወሰነ ኹነታ ላይ ተገናኘ፡፡
آية رقم 13
ﮅﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
ባለ ሳንቃዎችና ባለሚስማሮች በኾነችም ታንኳ ላይ ጫንነው፡፡
آية رقم 14
ﮋﮌﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
በጥበቃችን ስር ኾና ትንሻለላለች፡፡ ተክዶ ለነበረው ሰው ምንዳ (ይህንን ሠራን)፡፡
آية رقم 15
ﮒﮓﮔﮕﮖﮗ
ﮘ
ተዓምር አድርገንም በእርግጥ ተውናት፡፡ ከተገሳጭም አልለን?
آية رقم 16
ﮙﮚﮛﮜ
ﮝ
ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?
آية رقم 17
ቁርኣንንም ለመገንዘብ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገንዛቢም አልለን?
آية رقم 18
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
ዓድ አስተባበለች፡፡ ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ!
آية رقم 19
እኛ በእነርሱ ላይ ዘወትር መናጢ በኾነ ቀን በኀይል የምትንሻሻ ነፋስን ላክንባቸው፡፡
آية رقم 20
ﯘﯙﯚﯛﯜﯝ
ﯞ
ሰዎቹን ልክ ከሥሮቻቸው የተጎለሰሱ የዘንባባ ግንዶች መስለው (ከተደበቁበት) ትነቅላቸዋለች፡፡
آية رقم 21
ﯟﯠﯡﯢ
ﯣ
ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?
آية رقم 22
ቁርኣንንም ለማስታወስ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?
آية رقم 23
ﯬﯭﯮ
ﯯ
ሰሙድ በአስፈራሪዎቹ አስተባበለች፡፡
آية رقم 24
«ከእኛ የኾነን አንድን ሰው እንከተለዋለን? እኛ ያን ጊዜ በስህተትና በዕብደት ውስጥ ነን» አሉ፡፡
آية رقم 25
«ከኛ መካከል በእርሱ ላይ (ብቻ) ማስገንዘቢያ (ራእይ) ተጣለለትን? አይደለም እርሱ ውሸታም ኩሩ ነው» (አሉ)፡፡
آية رقم 26
ﰅﰆﰇﰈﰉ
ﰊ
ውሸታሙ ኩሩው ማን እንደኾነ ነገ በእርግጥ ያውቃሉ፡፡
آية رقم 27
እኛ ሴት ግመልን ለእነርሱ መፈተኛ ትኾን ዘንድ ላኪዎች ነን፡፡ ተጠባበቃቸውም፡፡ ታገስም፡፡
آية رقم 28
ውሃውንም በመካከላቸው የተከፈለ መኾኑን ንገራቸው፡፡ ከውሃ የኾነ ፋንታ ሁሉ (ተረኞቹ) የሚጣዱት ነው፡፡
آية رقم 29
ﭛﭜﭝﭞ
ﭟ
ጓደኛቸውንም ጠሩ፡፡ ወዲያውም (ሰይፍን) ተቀበለ፡፡ ወጋትም፡፡
آية رقم 30
ﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
ቅጣቴና ማስጠንቀቂያዎቼም እንዴት ነበሩ?
آية رقم 31
እኛ በእነርሱ ላይ አንዲትን ጩኸት ላክንባቸው፡፡ ወዲያውም ከበረት አጣሪ (አጥር) እንደ ተሰባበረ ርግጋፊ ኾኑ፡፡
آية رقم 32
ቁርኣንንም ለመገንዘብ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?
آية رقم 33
ﭶﭷﭸﭹ
ﭺ
የሉጥ ሕዝብ በአስፈራሪዎቹ አስተባበለች፡፡
آية رقم 34
እኛ በእነርሱ ላይ ጠጠርን ያዘለች ነፋስን ላክን፡፡ የሉጥ ቤተሰቦች ብቻ ሲቀሩ (እነርሱንስ) በሌሊት መጨረሻ ላይ አዳንናቸው፡፡
آية رقم 35
ከእኛ በኾነ ጸጋ (አዳንናቸው)፡፡ እንደዚሁ ያመሰገነን ሰው እንመነዳለን፡፡
آية رقم 36
ﮏﮐﮑﮒﮓ
ﮔ
ብርቱይቱን አያያዛችንንም በእርግጥ አስጠነቀቃቸው፡፡ በማስጠንቀቂያዎቹም ተከራከሩ፡፡
آية رقم 37
ከእንግዶቹም እንዲያስመቻቸው ደጋግመው ፈለጉት፡፡ ወዲያውም ዓይኖቻቸውን አበስን፡፡ «ቅጣቴንና ማስጠንቀቂያዎቼንም ቅመሱ» (አልናቸው)፡፡
آية رقم 38
ﮟﮠﮡﮢﮣ
ﮤ
በማለዳም ዘውታሪ የኾነ ቅጣት በእርግጥ ማለደባቸው፡፡
آية رقم 39
ﮥﮦﮧ
ﮨ
«ቅጣቴንና ማስጠንቀቂያዎቼንም ቅመሱ» (ተባሉ)፡፡
آية رقم 40
ቁርኣንንም ለመገንዘብ በእርግጥ አገራነው፡፡ ተገሳጭም አልለን?
آية رقم 41
ﮱﯓﯔﯕﯖ
ﯗ
የፈርዖንንም ቤተሰቦች ማስጠንቀቂያዎች በእርግጥ መጡዋቸው፡፡
آية رقم 42
በተዓምራቶቻችን በሁሏም አስተባበሉ፡፡ የብርቱ ቻይንም አያያዝ ያዝናቸው፡፡
آية رقم 43
ከሓዲዎቻችሁ ከእነዚህ በላጮች ናቸውን? ወይስ ለናንተ በመጽሐፎች ውስጥ (የተነገረ) ነፃነት አላችሁን?
آية رقم 44
ﯫﯬﯭﯮﯯ
ﯰ
ወይስ «እኛ የተረዳን ክምቹዎች ነን» ይላሉን?
آية رقم 45
ﯱﯲﯳﯴ
ﯵ
ክምቹዎቹ በእርግጥ ድል ይምመታሉ፡፡ ጀርባዎችንም ያዞራሉ፡፡
آية رقم 46
ﯶﯷﯸﯹﯺﯻ
ﯼ
ይልቁንም ሰዓቲቱ (ትንሣኤ) ቀጠሮዋቸው ናት፡፡ ሰዓቲቱም በጣም የከበደችና የመረረች ናት፡፡
آية رقم 47
ﯽﯾﯿﰀﰁ
ﰂ
አመጸኞች በስህተትና በእሳቶች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 48
በእሳት ውስጥ በፊቶቻቸው በሚጎተቱበት ቀን «የሰቀርን መንካት ቅመሱ» (ይባላሉ)፡፡
آية رقم 49
ﰍﰎﰏﰐﰑ
ﰒ
እኛ ሁሉን ነገር በልክ ፈጠርነው፡፡
آية رقم 50
ﭑﭒﭓﭔﭕﭖ
ﭗ
ትእዛዛችንም እንደ ዓይን ቅጽበት አንዲት (ቃል) እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 51
ﭘﭙﭚﭛﭜﭝ
ﭞ
ብጤዎቻችሁንም በእርግጥ አጠፋን፡፡ ተገሳጭም አልለን?
آية رقم 52
ﭟﭠﭡﭢﭣ
ﭤ
የሠሩትም ነገር ሁሉ በመጽሐፎች ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 53
ﭥﭦﭧﭨ
ﭩ
ትንሹም ትልቁም ሁሉ የተጻፈ ነው፡፡
آية رقم 54
ﭪﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
አላህን ፈሪዎቹ በአትክልቶችና በወንዞች ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 55
ﭰﭱﭲﭳﭴﭵ
ﭶ
(እነርሱም ውድቅ ቃልና መውወንጀል በሌለበት) በእውነት መቀመጫ ውስጥ ቻይ የሆነው ንጉሥ ዘንድ ናቸው፡፡
تقدم القراءة