ترجمة معاني سورة النجم باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
آية رقم 2

ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
آية رقم 4

እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 5

ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
آية رقم 6

የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
آية رقم 7

እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
آية رقم 8

ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
آية رقم 9

(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
آية رقم 10

ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
آية رقم 11

(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
آية رقم 12

ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
آية رقم 13

በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
آية رقم 14

በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
آية رقم 15

እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
آية رقم 16

ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
آية رقم 17

ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
آية رقم 18

ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
آية رقم 19

አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
آية رقم 20

ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
آية رقم 21

ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
آية رقم 22

ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡

እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
آية رقم 25

መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡

እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡

ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡

ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡

በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡

(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
آية رقم 33

ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
آية رقم 34

ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
آية رقم 35

የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
آية رقم 36

ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
آية رقم 37

በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
آية رقم 38

(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
آية رقم 40

ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
آية رقم 41

ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
آية رقم 42

መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
آية رقم 43

እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
آية رقم 44

እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
آية رقم 45

እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
آية رقم 46

ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
آية رقم 47

የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
آية رقم 48

እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
آية رقم 49

እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
آية رقم 50

እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
آية رقم 51

ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡

በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
آية رقم 53

የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
آية رقم 54

ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
آية رقم 55

ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
آية رقم 56

ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
آية رقم 57

ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
آية رقم 60

ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
آية رقم 61

እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
تقدم القراءة