ترجمة معاني سورة النجم باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﭑﭒﭓ
ﭔ
በኮከብ እምላለሁ በወደቀ (በገባ) ጊዜ፡፡
آية رقم 2
ﭕﭖﭗﭘﭙ
ﭚ
ነቢያችሁ (ሙሐመድ) አልተሳሳተም፤ አልጠመመምም፡፡
آية رقم 3
ﭛﭜﭝﭞ
ﭟ
ከልብ ወለድም አይናገርም፡፡
آية رقم 4
ﭠﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
እርሱ (ንግግሩ) የሚወርረድ ራእይ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 5
ﭦﭧﭨ
ﭩ
ኀይሎቹ ብርቱው (መልአክ) አስተማረው፡፡
آية رقم 6
ﭪﭫﭬ
ﭭ
የዕውቀት ባለቤት የኾነው (አስተማረው፤ በተፈጥሮ ቅርጹ ኾኖ በአየር ላይ) ተደላደለም፡፡
آية رقم 7
ﭮﭯﭰ
ﭱ
እርሱ በላይኛው አድማስ ኾኖ፡፡
آية رقم 8
ﭲﭳﭴ
ﭵ
ከዚያም ቀረበ፤ ወረደም፡፡
آية رقم 9
ﭶﭷﭸﭹﭺ
ﭻ
(ከእርሱ) የሁለት ደጋኖች ጫፍ ያህል ወይም (ከዚህ) ይበልጥ የቀረበ ኾነም፡፡
آية رقم 10
ﭼﭽﭾﭿﮀ
ﮁ
ወደ ባሪያውም (አላህ) ያወረደውን አወረደ፡፡
آية رقم 11
ﮂﮃﮄﮅﮆ
ﮇ
(ነቢዩም በዓይኑ) ያየውን ልቡ አልዋሸም፡፡
آية رقم 12
ﮈﮉﮊﮋ
ﮌ
ታዲያ በሚያየው ላይ ትከራከሩታላችሁን?
آية رقم 13
ﮍﮎﮏﮐ
ﮑ
በሌላይቱም መውረድ ጊዜ በእርግጥ አይቶታል፡፡
آية رقم 14
ﮒﮓﮔ
ﮕ
በመጨረሻይቱ ቁርቁራ አጠገብ፤
آية رقم 15
ﮖﮗﮘ
ﮙ
እርሷ ዘንድ መኖሪያይቱ ገነት ያለች ስትኾን፡፡
آية رقم 16
ﮚﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ቁርቁራይቱን የሚሸፍን ነገር በሚሸፍናት ጊዜ (አየው)፡፡
آية رقم 17
ﮠﮡﮢﮣﮤ
ﮥ
ዓይኑ (ካየው) አልተዘነበለም፡፡ ወሰንም አላለፈም፡፡
آية رقم 18
ﮦﮧﮨﮩﮪﮫ
ﮬ
ከጌታው ታምራቶች ታላላቆቹን በእርግጥ አየ፡፡
آية رقم 19
ﮭﮮﮯ
ﮰ
አል-ላትንና አል-ዑዛን አያችሁን?
آية رقم 20
ﮱﯓﯔ
ﯕ
ሦስተኛይቱንም አነስተኛዋን መናትን (አያችሁን? የምትግገዟቸው ኃይል አላቸውን?)
آية رقم 21
ﯖﯗﯘﯙ
ﯚ
ለእናንተ ወንድ ለእርሱም ሴት (ልጅ) ይኖራልን?
آية رقم 22
ﯛﯜﯝﯞ
ﯟ
ይህቺ ያን ጊዜ አድላዊ ክፍያ ናት፡፡
آية رقم 23
እነርሱ እናንተና አባቶቻችሁ (አማልክት ብላችሁ) የጠራችኋቸው ስሞች ብቻ እንጅ ምንም አይደሉም፡፡ አላህ በእርሷ (መግገዛት) ምንም ማስረጃ አላወረደም፡፡ ከጌታቸውም መምሪያ የመጣላቸው ሲኾኑ ጥርጣሬንና ነፍሶች የሚዘነበሉበትን እንጅ ሌላ አይከተሉም፡፡
آية رقم 24
ﯼﯽﯾﯿ
ﰀ
ለሰው የተመኘው ሁሉ አለውን?
آية رقم 25
ﰁﰂﰃ
ﰄ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም (ዓለም) የአላህ ብቻ ናቸው፡፡
آية رقم 26
በሰማያት ውስጥ ካለ መልአክም ብዙዎች (ሊማለዱለት) ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ከፈቀደ በኋላ ቢኾን እንጅ ምልጃቸው ምንም አትጠቅምም፡፡
آية رقم 27
እነዚያ በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት መላእክትን በሴት አጠራር ይጠራሉ፡፡
آية رقم 28
ለእነርሱም በእርሱ ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ ጥርጣሬን እንጅ ሌላን አይከተሉም፡፡ ጥርጣሬም ከእውነት ምንም አያብቃቃም፡፡
آية رقم 29
ከግሣጼያችንም (ከቁርኣን) ከሸሸና አነስተኛይቱን ሕይወት እንጅ ሌላን ከማይሻ ሰው ዙር (ተወው)፡፡
آية رقم 30
ይህ (አነስተኛይቱን ሕይወት መምረጥ) ከዕውቀት ድካቸው ነው፡፡ ጌታህ እርሱ ከመንገዱ የተሳሳተውን በእርግጥ ዐዋቂ ነው፡፡ እርሱም የቀናውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
آية رقم 31
በሰማያት ያለውና በምድር ያለው ሁሉ የአላህ ነው፡፡ እነዚያን ያጠፉትን በሠሩት ሊቀጣ እነዚያን ያሳመሩትንም በመልካሚቱ (ገነት) ሊመነዳ (የጠመመውንና የቀናውን ያውቃል)፡፡
آية رقم 32
(እነርሱ) እነዚያ የኃጢኣትን ታላለቆችና አስጸያፊዎቹን የሚርቁ ናቸው፡፡ ግን ትናንሾቹ የሚማሩ ናቸው፡፡ ጌታህ ምሕረተ ሰፊ ነውና፡፡ ከምድር በፈጠራችሁ ጊዜ እናንተም በእናቶቻችሁ ሆዶች ውስጥ ሽሎች በኾናችሁ ጊዜ እርሱ በናንተ (ኹነታ) ዐዋቂ ነው፡፡ ነፍሶቻችሁንም አታወድሱ እርሱ የሚፈራውን ሰው ዐዋቂ ነው፡፡
آية رقم 33
ﯢﯣﯤ
ﯥ
ያንን (ከእምነት) የዞረውን አየህን?
آية رقم 34
ﯦﯧﯨ
ﯩ
ጥቂትን የሰጠውንና ያቋረጠውንም (አየህን?)
آية رقم 35
ﯪﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
የሩቁ ምስጢር ዕውቀት እርሱ ዘንድ አልለን? ስለዚህ እርሱ ያያልን?
آية رقم 36
ይልቁንም በዚያ በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ ባለው ነገር አልተነገረምን?
آية رقم 37
ﯸﯹﯺ
ﯻ
በዚያም (የታዘዘውን) በፈጸመው በኢብራሂም (ጽሑፎች ውስጥ ባለው አልተነገረምን?)
آية رقم 38
ﯼﯽﯾﯿﰀ
ﰁ
(እርሱም ኃጢያት) ተሸካሚ ነፍስ የሌላይቱን ነፍስ ኃጢኣት አትሸከምም፡፡
آية رقم 39
ﰂﰃﰄﰅﰆﰇ
ﰈ
ለሰውም ሁሉ የሠራው እንጅ ሌላ የለውም፡፡
آية رقم 40
ﰉﰊﰋﰌ
ﰍ
ሥራውም ሁሉ ወደ ፊት ይታያል፡፡
آية رقم 41
ﰎﰏﰐﰑ
ﰒ
ከዚያም ሙሉውን ምንዳ ይመነዳዋል፡፡
آية رقم 42
ﰓﰔﰕﰖ
ﰗ
መጨረሻውም ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
آية رقم 43
ﰘﰙﰚﰛ
ﰜ
እነሆ እርሱም አስሳቀ፣ አስለቀሰም፡፡
آية رقم 44
ﰝﰞﰟﰠ
ﰡ
እነሆ እርሱም ገደለ፣ አስነሳም፡፡
آية رقم 45
ﭑﭒﭓﭔﭕ
ﭖ
እርሱም ሁለቱን ዓይነቶች ወንድንና ሴትን ፈጠረ፡፡
آية رقم 46
ﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ከፍትወት ጠብታ (በማህጸን ውስጥ) በምትፈሰስ ጊዜ፡፡
آية رقم 47
ﭜﭝﭞﭟ
ﭠ
የኋለኛይቱም ማስነሳት በእርሱ ላይ ነው፡፡
آية رقم 48
ﭡﭢﭣﭤ
ﭥ
እነሆ እርሱም አከበረ፣ ጥሪተኛም አደረገ፡፡
آية رقم 49
ﭦﭧﭨﭩ
ﭪ
እነሆ እርሱም የሺዕራ ጌታ ነው፡፡
آية رقم 50
ﭫﭬﭭﭮ
ﭯ
እነሆ እርሱም የፊተኛይቱን ዓድ አጥፍቷል፡፡
آية رقم 51
ﭰﭱﭲ
ﭳ
ሰሙድንም (አጥፍቷል)፤ አላስቀረምም፡፡
آية رقم 52
በፊትም የኑሕን ሕዝቦች (አጥፍቷል)፡፡ እነርሱ በጣም በደለኞችና እጅግ የጠመሙ እነርሱ ነበሩና፡፡
آية رقم 53
ﭿﮀ
ﮁ
የተገለበጠችውንም ከተማ ደፋ፡፡
آية رقم 54
ﮂﮃﮄ
ﮅ
ያለበሳትንም አለበሳት፡፡
آية رقم 55
ﮆﮇﮈﮉ
ﮊ
ከጌታህም ጸጋዎች በየትኛው ትጠራጠራለህ?
آية رقم 56
ﮋﮌﮍﮎﮏ
ﮐ
ይህ ከፊተኞቹ አስፈራሪዎች (ጎሳ) የኾነ አስፈራሪ ነው፡፡
آية رقم 57
ﮑﮒ
ﮓ
ቀራቢይቱ (ኅልፈተ ዓለም) ቀረበች፡፡
آية رقم 58
ﮔﮕﮖﮗﮘﮙ
ﮚ
ለእርሷ ከአላህ ሌላ ገላጭ የላትም፡፡
آية رقم 59
ﮛﮜﮝﮞ
ﮟ
ከዚህ ንግግር ትደነቃላችሁን?
آية رقم 60
ﮠﮡﮢ
ﮣ
ትስቃላችሁምን? አታለቅሱምን?
آية رقم 61
ﮤﮥ
ﮦ
እናንተም ዘንጊዎች ናችሁ፡፡
آية رقم 62
ﮧﮨﮩﮪ
ﮫ
ለአላህም ስገዱ ተገዙትም፡፡
تقدم القراءة