ترجمة معاني سورة المدّثر باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
آية رقم 2

ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
آية رقم 3

ጌታህንም አክብር፡፡
آية رقم 4

ልብስህንም አጥራ፡፡
آية رقم 5

ጣዖትንም ራቅ፡፡
آية رقم 6

ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
آية رقم 7

ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
آية رقم 8

በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
آية رقم 9

ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
آية رقم 10

በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
آية رقم 11

አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
آية رقم 12

ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
آية رقم 13

(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
آية رقم 14

ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
آية رقم 15

ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
آية رقم 16

ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
آية رقم 17

በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
آية رقم 18

እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
آية رقم 19

ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
آية رقم 20

ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
آية رقم 21

ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
آية رقم 22

ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
آية رقم 23

ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
آية رقم 24

አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 25

«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
آية رقم 26

በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
آية رقم 27

ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
آية رقم 28

(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
آية رقم 29

ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
آية رقم 30

በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡

የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
آية رقم 32

(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
آية رقم 33

በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
آية رقم 34

በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
آية رقم 35

እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
آية رقم 36

ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
آية رقم 37

ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
آية رقم 38

ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
آية رقم 39

የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
آية رقم 40

(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
آية رقم 41

ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
آية رقم 42

(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
آية رقم 43

(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
آية رقم 44

«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
آية رقم 45

«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
آية رقم 46

«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
آية رقم 47

«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
آية رقم 48

የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
آية رقم 49

ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
آية رقم 50

እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡

ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
آية رقم 53

ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
آية رقم 54

ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
آية رقم 55

ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡

አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
تقدم القراءة