ترجمة معاني سورة المدّثر باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation
ﰡ
آية رقم 1
ﮪﮫ
ﮬ
አንተ (ልብስህን) ደራቢው ሆይ!
آية رقم 2
ﮭﮮ
ﮯ
ተነሳ አስጠንቅቅም፡፡
آية رقم 3
ﮰﮱ
ﯓ
ጌታህንም አክብር፡፡
آية رقم 4
ﯔﯕ
ﯖ
ልብስህንም አጥራ፡፡
آية رقم 5
ﯗﯘ
ﯙ
ጣዖትንም ራቅ፡፡
آية رقم 6
ﯚﯛﯜ
ﯝ
ማብዛትንም የምትፈልግ ኾነህ፤ (በረከትን) አትለግስለለ
آية رقم 7
ﯞﯟ
ﯠ
ለጌታህም (ትዕዛዝ) ታገሥ፡፡
آية رقم 8
ﯡﯢﯣﯤ
ﯥ
በቀንዱም በተነፋ ጊዜ (ነገሩ ይበረታል)፡፡
آية رقم 9
ﯦﯧﯨﯩ
ﯪ
ይህም (ጊዜ) ያ ቀን አስቸጋሪ ቀን ነው፡፡
آية رقم 10
ﯫﯬﯭﯮ
ﯯ
በከሓዲዎች ላይ ገር ያልኾነ ነው፡፡
آية رقم 11
ﯰﯱﯲﯳ
ﯴ
አንድ ኾኖ ከፈጠርኩት ሰው ጋር ተዎኝ (እኔ እበቃሃለሁ)፡፡
آية رقم 12
ﯵﯶﯷﯸ
ﯹ
ለእርሱም የተዘረጋን ገንዘብ (በያይነቱ) ያደረግሁለት፡፡
آية رقم 13
ﯺﯻ
ﯼ
(በያደባባዩ) ተገኝዎች የኾኑ ወንዶች ልጆችንም፡፡
آية رقم 14
ﯽﯾﯿ
ﰀ
ለእርሱም (ኑሮውን) መዘርጋትን የዘረጋሁለት (ከኾነ ሰው ገር ተዎኝ)፡፡
آية رقم 15
ﰁﰂﰃﰄ
ﰅ
ከዚያም ልጨምርለት ይከጅላል፡፡
آية رقم 16
ﰆﰇﰈﰉﰊﰋ
ﰌ
ይከልከል፤ እርሱ ለአንቀጾቻችን በእርግጥ ተቃዋሚ ነበር፡፡
آية رقم 17
ﰍﰎ
ﰏ
በእርግጥ ችግርን አስገድደዋለሁ፡፡
آية رقم 18
ﰐﰑﰒ
ﰓ
እርሱ (በቁርኣን ነገር) ሐሰበ፤ ገመተም፡፡
آية رقم 19
ﭑﭒﭓ
ﭔ
ተረገመም፤ እንዴት ገመተ!
آية رقم 20
ﭕﭖﭗﭘ
ﭙ
ከዚያም (ከሞት በኋላ) ተረገመ፡፡ እንዴት ገመተ!
آية رقم 21
ﭚﭛ
ﭜ
ከዚያም እንደ ገና (በቁርኣኑ ነገር) ተመለከተ፡፡
آية رقم 22
ﭝﭞﭟ
ﭠ
ከዚያም ፊቱን አጨፈገገ፤ አኮማተረም፡፡
آية رقم 23
ﭡﭢﭣ
ﭤ
ከዚያም (ከማመን) ዞረ፤ ኮራም፡፡
آية رقم 24
ﭥﭦﭧﭨﭩﭪ
ﭫ
አለም «ይህ (ከሌላ) የሚቀዳ ድግምት እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
آية رقم 25
ﭬﭭﭮﭯﭰ
ﭱ
«ይህ የሰው ቃል እንጅ ሌላ አይደለም፡፡»
آية رقم 26
ﭲﭳ
ﭴ
በሰቀር ውስጥ በእርግጥ አገባዋለሁ፡፡
آية رقم 27
ﭵﭶﭷﭸ
ﭹ
ሰቀር ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
آية رقم 28
ﭺﭻﭼﭽ
ﭾ
(ያገኘችውን ሁሉ) አታስቀርም አትተውምም፡፡
آية رقم 29
ﭿﮀ
ﮁ
ቆዳን በጣም አክሳይ ናት፡፡
آية رقم 30
ﮂﮃﮄ
ﮅ
በእርሷም ላይ አሥራ ዘጠኝ (ዘበኞች) አሉባት፡፡
የእሳትንም ዘበኞች መላእክት እንጅ ሌላ አላደረግንም፡፡ ቁጥራቸውንም ለእነዚያ ለካዱት መፈተኛ እንጅ አላደረግንም፡፡ እነዚያ መጽሐፍን የተሰጡት እንዲያረጋግጡ፣ እነዚያም ያመኑት እምነትን እንዲጨምሩ፣ እነዚያም መጽሐፍን የተሰጡትና ምእምናኖቹ እንዳይጠራጠሩ፣ እነዚያም በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው (መናፍቃን)፣ ከሓዲዎችም አላህ በዚህ (ቁጥር) ምን ምሳሌ ሽቷል? እንዲሉ (እንጅ አላደረግንም)፡፡ እንደዚሁ አላህ የሚሻውን ያጠምማል፡፡ የሚሻውንም ያቀናል፡፡ የጌታህንም ሰራዊት (ልክ) ከርሱ በቀር ማንም አያውቅም፡፡ እርሷም (የሰቀር እሳት) ለሰዎች መገሰጫ እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
آية رقم 32
ﯥﯦ
ﯧ
(ከክህደት) ይከልከሉ፡፡ በጨረቃ እምላለሁ፡፡
آية رقم 33
ﯨﯩﯪ
ﯫ
በሌሊቱም በኼደ ጊዜ፡፡
آية رقم 34
ﯬﯭﯮ
ﯯ
በንጋቱም ባበራ ጊዜ፡፡
آية رقم 35
ﯰﯱﯲ
ﯳ
እርሷ (ሰቀር) ከታላላቆቹ (አደጋዎች) አንዷ ናት፡፡
آية رقم 36
ﯴﯵ
ﯶ
ለሰዎች አስፈራሪ ስትኾን፡፡
آية رقم 37
ከእናንተ (ወደ በጎ ነገር) መቅደምን ወይም ወደ ኋላ መቅረትን ለሻ ሰው (አስፈራሪ ስትኾኑ)፡፡
آية رقم 38
ﯿﰀﰁﰂﰃ
ﰄ
ነፍስ ሁሉ በሠራችው ሥራ ተያዥ ናት፡፡
آية رقم 39
ﰅﰆﰇ
ﰈ
የቀኝ ባለቤቶች ብቻ ሲቀሩ፡፡
آية رقم 40
ﰉﰊﰋ
ﰌ
(እነርሱስ) በገነቶች ውስጥ ይጠያየቃሉ፡፡
آية رقم 41
ﰍﰎ
ﰏ
ከአመጸኞቹ ኹነታ፡፡
آية رقم 42
ﰐﰑﰒﰓ
ﰔ
(ይሏቸዋልም) «በሰቀር ውስጥ ምን አገባችሁ?»
آية رقم 43
ﰕﰖﰗﰘﰙ
ﰚ
(እነርሱም) ይላሉ «ከሰጋጆቹ አልነበርንም፡፡
آية رقم 44
ﰛﰜﰝﰞ
ﰟ
«ለድኾችም የምናበላ አልነበርንም፡፡
آية رقم 45
ﰠﰡﰢﰣ
ﰤ
«ከዘባራቂዎቹም ጋር እንዘባርቅ ነበርን፡፡
آية رقم 46
ﰥﰦﰧﰨ
ﰩ
«በፍርዱ ቀንም እናስተባብል ነበርን፡፡
آية رقم 47
ﰪﰫﰬ
ﰭ
«እርግጠኛው (ሞት) እስከ መጣን ድረስ፡፡»
آية رقم 48
ﭑﭒﭓﭔ
ﭕ
የአማላጆችም ምልጃ አትጠቅማቸውም፡፡
آية رقم 49
ﭖﭗﭘﭙﭚ
ﭛ
ከግሣጼዬም (ከቁርኣን) የሚያፈገፍጉት ለእነርሱ ምን አልላቸው?
آية رقم 50
ﭜﭝﭞ
ﭟ
እነርሱ ልክ ደንባሪዎች የሜዳ አህዮች ይመስላሉ፡፡
آية رقم 51
ﭠﭡﭢ
ﭣ
ከዐንበሳ የሸሹ፡፡
آية رقم 52
ይልቁንም ከእነርሱ እያንዳንዱ ሰው ሁሉ የተዘረጉ ጽሑፎችን እንዲስሰጥ ይፈልጋል፡፡
آية رقم 53
ﭮﭯﭰﭱﭲﭳ
ﭴ
ይከልከሉ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻይቱን ዓለም (ቅጣት) አይፈሩም፡፡
آية رقم 54
ﭵﭶﭷ
ﭸ
ይከልከሉ፡፡ እርሱ (ቁርኣን) መገሠጫ ነው፡፡
آية رقم 55
ﭹﭺﭻ
ﭼ
ስለዚህ የሻ ሰው ይገሰጽበታል፡፡
آية رقم 56
አላህም ካልሻ በስተቀር አይገሠጹም፡፡ እርሱ (አላህ) የመፈራት ባለቤት የምሕረትም ባለቤት ነው፡፡
تقدم القراءة