ترجمة معاني سورة الواقعة باللغة الأمهرية من كتاب Sadiq and Sani - Amharic translation

Sadiq and Sani - Amharic translation

آية رقم 1


መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡
آية رقم 2

ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡
آية رقم 3

ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡
آية رقم 4

ምድር መናወጥን በተናወጠች ጊዜ፡፡
آية رقم 5

ተራራዎችም መፍፈርፈርን በተፈረፈሩ ጊዜ (እንደተፈጨ ዱቄት በኾኑ ጊዜ)፡፡
آية رقم 6

የተበተነ ብናኝ በኾኑም ጊዜ
آية رقم 7

ሦስት ዓይነቶችም በኾናችሁ ጊዜ (ታዋርዳለች፤ ታነሳለችም)፡፡
آية رقم 8

የቀኝ ጓዶችም ምን (የተከበሩ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
آية رقم 9

የግራ ጓዶችም ምን (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
آية رقم 10

(ለበጎ ሥራ) ቀዳሚዎቹም (ለገነት) ቀዳሚዎች ናቸው፡፡
آية رقم 11

እነዚያ ባለሟሎቹ ናቸው፡፡
آية رقم 12

በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ሲኾኑ፡፡
آية رقم 13

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
آية رقم 14

ከኋለኞቹም ጥቂቶች ናቸው፡፡
آية رقم 15

በተታቱ አልጋዎች ላይ ይኾናሉ፡፡
آية رقم 16

በእርሷ ላይ የተመቻቹና ፊት ለፊት የተቅጣጩ ሲኾኑ፡፡
آية رقم 17

በእነርሱ ላይ ሁል ጊዜ የማያረጁ ወጣቶች ልጆች ይዘዋወራሉ፡፡
آية رقم 18

ከጠጅ ምንጭም በብርጭቆዎችና በኩስኩስቶች በጽዋም (በእነርሱ ላይ ይዝዞራሉ)፡፡
آية رقم 19

ከእርሷ የራስ ምታት አያገኛቸውም፤ አይሰክሩምም፡፡
آية رقم 20

ከሚመርጡትም ዓይነት በእሸቶች፡፡
آية رقم 21

ከሚሹትም በኾነ የበራሪ ሥጋ (ይዞሩባቸዋል)፡፡
آية رقم 22

ዓይናማዎች የኾኑ ነጫጭ ቆንጆዎችም አሏቸው፡፡
آية رقم 23

ልክ እንደተሸፈነ ሉል መሰሎች የኾኑ፡፡
آية رقم 24

በዚያ ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ዋጋ ይኾን ዘንድ (ይህንን አደረግንላቸው)፡፡
آية رقم 25

በውስጥዋ ውድቅ ንግግርንና መውወንጀልን አይሰሙም፡፡
آية رقم 26

ግን ሰላም መባባልን (ይሰማሉ)፡፡
آية رقم 27

የቀኝም ጓዶች ምንኛ (የከበሩ) የቀኝ ጓዶች!
آية رقم 28

በተቀፈቀፈ (እሾህ በሌለው) ቁርቁራ ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 29

(ፍሬው) በተነባበረ በሙዝ ዛፍም፡፡
آية رقم 30

በተዘረጋ ጥላ ሥርም፡፡
آية رقم 31

በሚንቧቧ ውሃ አጠገብም፡፡
آية رقم 32

ብዙ (ዓይነት) በኾኑ ፍራፍሬዎችም፡፡
آية رقم 33

የማትቋረጥም የማትከለከልም የኾነች፡፡
آية رقم 34

ከፍ በተደረጉ ምንጣፎችም (ሴቶችም መካከል)፡፡
آية رقم 35

እኛ አዲስ ፍጥረት አድርገን (ለእነርሱ) ፈጠርናቸው፡፡
آية رقم 36

ደናግሎችም አደረግናቸው፡፡
آية رقم 37

ለባሎቻቸው ተሽሞርሟሪዎች እኩያዎች (አደረግናቸው)፡፡
آية رقم 38

ለቀኝ ጓዶች (አዘጋጀናቸው)፡፡
آية رقم 39

ከፊተኞቹ ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
آية رقم 40

ከኋለኞቹም ብዙ ጭፍሮች ናቸው፡፡
آية رقم 41

የግራ ጓደኞችም ምንኛ (የተዋረዱ) የግራ ጓዶች! ናቸው፡፡
آية رقم 42

በመርዛም ነፋስ በጣም በፈላ ውሃም ውስጥ ናቸው፡፡
آية رقم 43

ከጥቁር ጭስም በኾነ ጥላ ውስጥ፡፡
آية رقم 44

ቀዝቃዛም መልካምም ያልኾነ፡፡
آية رقم 45

እነርሱ ከዚህ በፊት ቅምጥሎች ነበሩና፡፡
آية رقم 46

በታላቅ ኀጢአትም ላይ ይዘወትሩ ነበሩና፡፡

ይሉም ነበሩ፡- «በሞትንና ዐፈር፣ ዐጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ በእርግጥ የምንቀሰቀስ ነን?
آية رقم 48

«የፊተኞቹ አባቶቻችንም?»
آية رقم 49

በላቸው፡- «ፊተኞቹም ኋለኞቹም፡፡
آية رقم 50

«በተወሰነ ቀን ቀጠሮ በእርግጥ ተሰብሳቢዎች ናቸው፡፡
آية رقم 51

«ከዚያም እናንተ ጠማሞች አስተባባዮች ሆይ!
آية رقم 52

« ከዘቁም ዛፍ በእርግጥ በይዎች ናችሁ፡፡
آية رقم 53

«ከእርሷም ሆዶቻችሁን ሞይዎች ናችሁ፡፡
آية رقم 54

«በእርሱ ላይም ከፈላ ውሃ ጠጪዎች ናችሁ፡፡
آية رقم 55

«የተጠሙንም ግመሎች አጠጣጥ ብጤ ጠጪዎች ናችሁ፡፡»
آية رقم 56

ይህ በፍርዱ ቀን መስተንግዷቸው ነው፡፡
آية رقم 58

(በማኅፀኖች) የምታፈሱትን አያችሁን?
آية رقم 59

እናንተ ትፈጥሩታላችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎቹን ነን?
آية رقم 60

እኛ ሞትን (ጊዜውን) በመካከላችሁ ወሰንን፡፡ እኛም ተሸናፊዎች አይደለንም፡፡

ብጤዎቻችሁን በመለወጥና በዚያ በማታውቁትም (ቅርጽ) እናንተን በመፍጠር ላይ (አንሸነፍም)፡፡
آية رقم 62

የፊተኛይቱንም አፈጣጠር በእርግጥ ዐውቃችኋል፡፡ አትገነዘቡምን?
آية رقم 63

የምትዘሩትንም አያችሁን?
آية رقم 64

እናንተ ታበቅሉታላችሁን? ወይስ እኛ አብቃዮቹ ነን?
آية رقم 65

ብነሻ ኖሮ ደረቅ ስብርብር ባደረግነውና የምትደነቁም በኾናችሁ ነበር፡፡
آية رقم 66

«እኛ በዕዳ ተያዦች ነን፡፡
آية رقم 67

«በእርግጥም እኛ (ከመጠቀም) የተከለከልን ነን» (ትሉ ነበር)፡፡
آية رقم 68

ያንንም የምትጠጡትን ውሃ አየችሁን?
آية رقم 69

እናንተ ከደመናው አወረዳችሁትን? ወይስ እኛ አውራጆቹ ነን?
آية رقم 70

ብንሻ ኖሮ መርጋጋ ባደረግነው ነበር፡፡ አታመሰግኑምን?
آية رقم 71

ያቺንም የምትሰብቋትን እሳት አያችሁን?
آية رقم 72

እናንተ ዛፏን ፈጠራችሁን? ወይስ እኛ ፈጣሪዎችዋ ነን?
آية رقم 73

እኛ (ለገሀናም) ማስታወሻ ለመንገደኞችም መጠቀሚያ አደረግናት፡፡
آية رقم 74

የታላቁን ጌታህንም ስም አወድስ፡፡
آية رقم 75

በከዋክብትም መጥለቂያዎች እምላለሁ፡፡
آية رقم 77

እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
آية رقم 78

በተጠበቀ መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡
آية رقم 79

የተጥራሩት እንጅ ሌላ አይነካውም፡፡
آية رقم 80

ከዓለማት ጌታ የተወረደ ነው፡፡
آية رقم 81

በዚህ ንግግር እናንተ ቸልተኞች ናችሁን?
آية رقم 82

ሲሳያችሁንም (ዝናምን) እናንተ የምታስተባብሉት ታደርጋላችሁን?
آية رقم 83

(ነፍስ) ጉረሮንም በደረሰች ጊዜ፡፡
آية رقم 84

እናንተ ያን ጊዜ የምታዩ ስትኾኑ፡፡
آية رقم 85

እኛም ግን አታዩም እንጅ ከእናንተ ይልቅ ወደእርሱ የቀረብን ስንኾን፡፡
آية رقم 87

እውነተኞች እንደ ኾናችሁ (ነፍሲቱን ወደ አካሉ) ለምን አትመልሷትም፡፡
آية رقم 89

(ለእርሱ) ዕረፍት፣ መልካም ሲሳይም፣ የመጠቀሚያ ገነትም አልለው፡፡
آية رقم 91

ከቀኝ ጓዶች ስለ ኾንክ ላንተ ሰላም አልለህ (ይባላል)፡፡
آية رقم 93

ከፈላ ውሃ የኾነ መስተንግዶ አልለው፡፡
آية رقم 94

በገሀነም መቃጠልም (አልለው)፡፡
آية رقم 96

የታላቁንም ጌታህን ስም አወድስ፡፡
تقدم القراءة